የጤና ፈርስት ፕላስ የውል ስምምነት ( Laboratory Vendor Agreement )
May 27, 2026 ©
, ኢትዮጵያ
ይህ ስምምነት በጤና ፈርስት ፕላስ ("Telemedicine Platform"): የቴሌ ህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ፕላትፎርም, አድራሻ:22 ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 ልዩ ስሙ ማሪያ ሮቫቶ ካቶሊክ ት/ቤት በሻ ህንፃ 3ኛ ፎቅ 310 ፣ ስልክ: 0116 685858 ፣ email: contact@tenafirst.com, እና (ከዚህ በኋላ ተብሎ በሚጠራው) አድራሻ:- ክ/ከ ወረዳ የቤት ቁጥር ስልክ ቁጥር፡ ኢሜል: መካከል የተደረገ የውል ስምምነት የሚመለከት ነው ፡፡
አንቀጽ አንድ
የውሉ ዓላማ
1. ጤና ፈርስት ፕላስ የቴሌ ሕክምና መስጫ ፕላትፎርም ሲሆን ታካሚዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በታወቁ የጤና ባለሞያዎች 6037 ላይ በመደወል ወይንም ጤና ፈርስት ፕላስ የሞባይል መተግበሪያ ዳዉንሎድ በማድረግ የህክምና አገልግሎቶችን ቀላል እና ምቹ በሆነ መንገድ በመስጠት ላይ ይገኛል።
በተጨማሪም ከሌሎች የጤና እንክብካቤ አቅራቢዎች እንደ አምቡላስ፣ ላቡራቶሪዎች፣ ፋርማሲዎች፣ ክሊኒኮች፣ ሆስፒታሎች ጋር በማገናኘት የህክምና እና የምክር አገልግሎት የሚያገኙበት ቴክኖሎጂ ነው።
የዚህም ዉል አላማ ጤና ፈርስት ፕላስ ከ ጋር በአብሮነት በመስራት በጤና ፈርስት ፕላስ ፕላትፎርም በኩል ለሚመጡ ተገልጋዮች የላቦራቶሪ አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል ነዉ።
አንቀጽ ሁለት
ትርጓሜ
2.1 በዚህ ውል ውስጥ በግልጽ ካልተጠቀሰ በስተቀር የሚከተሉት ቃላቶች እና አገላለፆች የሚከተለውን ትርጉም ይኖራቸዋል፡፡
2.1.1 “ውል" ወይም “ስምምነት" ማለት በውል ሰጪ እና በውል ተቀባይ መካከል የተደረገን ይህ ውል እና ከዚህ ውል ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ሰነዶች እና በአባሪነት የተያያዙትን ሰነዶች ይጨምራል፡፡
2.1.2 “የውል ሰነድ" ማለት በዚህ ውስጥ የተዘረዘሩ ሰነዶችን ፤አባሪዎችን፤ ማሻሻያዎች እና ማራዘሚያዎችን ያካትታል፤
2.1.3 "አገልግሎቶች" ማለት የጤና ፈርስት ፕላስ የቴሌ ሕክምና ፕላት ፎርም አገልግሎት እና ከዚህ ውል ጋር ተያያዥነት ያላቸው የኢሜይል, አጭር የኤስ.ኤም.ኤስ መልክት ልውውጦች፣ ሪማይንደሮች ማንኛውም አገልግሎቶች ማለት ነው፡፡
2.1.4 "ቀን" ማለት ተከታታይ የቀን መቁጠሪያ ቀናቶች ማለት ነው፡፡ይህም ማለት የታካሚዉ ናሙና ከተሰጠበት ሰአት ጀምሮ የምርመራዉ ዉጤት በዉል ተቀባዪ የተላከበት ሰአት።
2.1.5 “ውል ተቀባይ” ማለት በውሉ ውስጥ በተጠቀሰው መሰረት ማለት ነው፡፡
2.1.6 “ውል ሰጪ” ማለት በዚህ ዉል መሰረት ጤና ፈርስት ፕላስ ማለት ነው፡፡
2.1.7 “ሚስጥራዊ መረጃዎች/confidential information" ማለት የታካሚዉ ሚስጥር ነው ተብሎ የታሰቡ መረጃዎች በሙሉ ማለት ነው::
2.1.8 “ግጭት” ማለት ከውል የሚመነጭ ማናቸውም አይነት ክርክር ወይም የይገባኛል ጥያቄዎች ናቸው፡፡
2.1.9 “ከአቅም በላይ የሆነ ችግር" ማለት ሁኔታዎች ወይም ክስተቶች ከተዋዋይ ወገኖች ቁጥጥር ውጪ የሆነ ያልታሰበ፤ሊወገድ የማይችል እና መነሻው በተዋዋይ ወገኖች ቸልተኝነት ወይም ጥንቃቄ በጎደለው ተግባር ባልሆነ እና ተዋዋይ ወገኖች ግዴታቸውን እንዳይወጡ የሚከለክላቸው ሁኔታ ሲሆን እነዚህም ሁኔታዎች ጦርነት ፤ብጥብጥ (አብዮት) ፤እሳት አደጋ ፤ ጎርፍ የመሬት መንቀጥቀጥ ፤ ማዕቀብ በቀጥታ እና ጉዳት ሲያስከትል በሚችል መልኩ የዚህን ውል መፈፀም የሚከለክሉ ሲሆኑ ነው፡፡
2.1.10 " የአገልግሎት መዝገባ ክፍያ " ውል ተቀባዩ የውል ሰጪውን የቴሌ ሕክምና ፕላት ፎርም አገልግሎት ለመጠቀም የሚከፍለው የአገልግሎት ክፍያ ሲሆን ይህም የተለያየ የጊዜ እርዝማኔ ይኖረዋል።
2.1.11 “የላቦራቶሪ ትእዛዝ/Testes Requested”፤ ሃኪሙ ለህክምናዉ ይረዳኛል ብሎ ያዘዘዉ ማንኛዉም የምርመራ ትእዛዞችን ያጠቃልላል።
2.1.12 “የትእዛዙ መለያ ቁጥር/order ID”፤ ታካሚዉ ምርመራ ሲታዘዝለት ከዉል ሰጪዉ ፕላትፎርም የሚሰጠው ከሌላው ትእዛዝ የሚለይበት ኮድ/ቁጥር ነው።
2.1.13 “የሃኪሙ መረጃ/Doctor’s information” የሃኪሙን ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር ይይዛል።
2.1.14 "የምርመራ ዉጤት/investigation result”፤ታካሚው ናሙናዉን ከሰጠ በኋላ የሚኖረዉ የላቦራቶሪ ምላሽ/ዝርዝር ዉጤት ነዉ።
2.1.15 የታካሚዉ መረጃዎች(patient information)፤ የታካሚዉ ስም፣ እድሜ፣ ስልክ ቁጥር፣ ጾታ፣ የላቦራቶሪ ትእዛዝ፣ የምርመራ ዉጤትን ያጠቃልላል።
2.1.16 “ናሙና/sample”፤ ታካሚዉ የህክምናው ባለሙያ ባዘዘዉ መሰረት በአካል ተገኝቶ የሚሰጠው ማንኛዉም የሰዉነት ተዋጾ ነዉ።
አንቀጽ ሦስት
የውል ሰነዶች ዝርዝር
3.1. ከዚህ በመቀጠል የተዘረዘሩት ሰነዶች የዚህ ውል አካል ተደርገው ይቆጠራሉ፡፡
ሀ) ይህ የውል ስምምነት፤
ለ) የዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ፤
ሐ) የኢሜይል ልውውጦች
መ) አጭር የስልክ መልእክት ልዉዉጦች
አንቀጽ አራት
የውል ስምምነቱ አጠቃላይ ወሰን፤
4.1. ውል ሰጪ የቴሌ ህክምና ፕላት ፎርምን በመጠቀም በፕላትፎርሙ በሚሰሩ የህክምና ባለሙያዎች የሚታዘዝ የላቦራቶሪ ትእዛዞች በጤናላብ(TenaLab) በሚባለዉ አፕሊኬሽን ወይም መተግበሪያ በመጠቀም ወደ ውል ተቀባዩ የላብራቶሪ ተቋም እንዲደርስ ያደርጋል።
ዉል ተቀባዩ የላብራቶሪ ተቋም የላቦራቶሪ ትዕዛዙን በመቀበል ተቀብሎም የምርመራ ውጤቱን በሚያስፈልገዉ አግባብ ጤናላብ (TenaLab) በሚባለዉ አፕሊኬሽን ወይም መተግበሪያ በመጠቀም ትዕዛዙን ወዳቀረበዉ የህክምና ባለሙያ ያስተላልፋል።
4.2. የዉል ሰጪን ፕላት ፎርም በመጠቀም የላቦራቶሪ አገልግሎት ለመስጠት ውል ተቀባይ ከውል ሰጪው የአገልግሎት መዝገባ ክፍያ በመረጠው አማራጭ እና የጊዜ ርዝማኔ መሰረት ቅድሚያ ክፍያን በመፈፀም አገልግሎቱን መስጠት መጀመር ይችላል።
የክፍያውም ሂደት:-
የኮንትራት(subscription) ክፍያ - የዉል ተቀባዩም የሚከተሉትን የኮንትራት ዕቅዶች መሰረት በማድረግ ለጤና ፈርስት ፕላስ (TenaFirst Plus) ክፍያ ያደርጋል።
የዉል ተቀባዩም የመረጡት ክፍያ:-
አንቀጽ አምስት
የውል ሰጪ ግዴታዎች
በዚህ ውል የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ውል ሰጪው ከዚህ ቀጥሎ የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩታል፡-
5.1. ውል ሰጪ አገልግሎቱን በተቀላጠፈና ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ ለውል ተቀባይ በሚፈለገው መጠን እና ጥራት መሰረት አሟልቶ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
5.2. ለውል ተቀባይ የአጠቃቀም እና የቴክኒካል ድጋፍ ለስራ ባልደረቦች ሁሉ በቪዲዮ የተደገፈ የፕላት ፎርሙ አጠቃቀም እገዛ ያደርጋል፡፡ችግር በሚገጥምበት ጊዜም ባስቸኳይ የቴክኒካል ድጋፍ ያደርጋል፡፡
5.3. ውል ሰጪ ለውል ተቀባይ ለ አገልግሎት በከፈለው የጊዜ ገደብ ውስጥ ተገቢውን የሆነ አገልግሎት የመስጠት ኃላፊነት አለበት።
5.4. ውል ሰጪው ዘመኑን የዋጀ ለተጠቃሚዎች ምቹ እና አስተማማኝ የሆነ የክፍያ ስርዓት መዘርጋት ይኖርበታል፡፡
5.5. የውል ሰጪው የታካሚዎቹን መረጃ(patient information) በተገቢው መንገድ የመጠበቅ እና ደህንነቱን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት፡፡
5.6. ውል ሰጪው ከአገልግሎት ያገኘውን ክፍያ የሥራ ግብር ለመንግስት ገቢ ያደርጋል፡፡
5.7. ውል ሰጪው ለተቀበለው ክፍያ ደረሰኝ የመስጠት ኃላፊነት አለበት፡፡
5.8 . የውሉ ዋጋ እንዳስፈላጊነቱ ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
5.9. ውል ሰጪው የዋጋ ለውጥ ካለ ከ30 ቀናቶች በፊት ለውል ተቀባይ በኢሜይል ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡
አንቀጽ ስድስት
የውል ተቀባይ ግዴታዎች
6.1. ውል ተቀባይ በውል ሰጪ በሚቀበለው የላቦራቶሪ ትእዛዝ መሰረት ተገልጋዮችን ወይም ታካሚዎችን ያለምንም እንግልት የማስተናገድ ግዴታ አለበት፡፡
6.2. ውል ተቀባዩም ተገልጋዩ ወይም ታካሚዉ የተጠቀመዉን የአገልግሎት ክፍያ ከታካሚዉ በቀጥታ መቀበል ይኖርበታል።
6.3. የውል ተቀባዩ በውል ሰጪ ፕላትፎርም ላይ የሚያስገባቸው የታካሚዉ መረጃዎች(patient information) የራሱ እና ትክክኛነቱን የማረጋገጥ ኃላፊነት የራሱ ይሆናል፡፡ ይህ ሆኖ ሳይቀር ለሚፈጠረው የህክምና ስህተት ኃላፊነቱን ይወስዳል፡፡
6.4. ውል ተቀባይ የአገልግሎት ለውጥ ወይም የክፍያ ለውጥ የማድረግ ሙሉ መብት አለው፡፡
6.5. ውል ተቀባይ የሥራ ፍቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ ሊኖረው ይገባል፡፡ ይህ ሆኖ ሳይቀር ለሚፈጠረው ችግር ውል ሰጪው ኃላፊነቱን አይወስድም፡፡
6.6. ውል ተቀባይ በንግድ ፍቃድ እና በንግድ ስያሜ የተፈቀደለትን አገልግሎቶች ብቻ በውል ሰጪ ፕላትፎርም አገልግሎቱን ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ ይህ ሆኖ ሳይቀር ለሚፈጠረው ችግር ውል ተቀባይ ኃላፊነቱን ይወስዳል፡፡
6.7. የዉል ተቀባዩም ናሙናውን በተቀበለበት በሶስት (3) ቀናት ውስጥ ትክክለኛ እና ወቅታዊ የምርመራ ሪፖርቶችን ትዕዛዙን ላቀረበዉ የህክምና ባለሙያ መላክ አለበት።
6.8. የዉል ተቀባዩ በጤና ፊርስት ፕላስ አፕሊኬሽን የተቀበለዉን የምርመራ ትእዛዝ በታዘዘዉ መሰረት እና በአግባቡ መመለሱን ማረጋገጥ አለበት።ይህ ሆኖ ሳይቀር ለሚፈጠረው ችግር ውል ተቀባይ ኃላፊነቱን ይወስዳል፡፡
6.9. የውል ተቀባዩ የታካሚ መረጃ(patient information), የላብራቶሪ ትዕዛዝና(Testes requested) ውጤት ሚስጥራዊነትን (confidential information) በተገቢው መንገድ የመጠበቅ እና ደህንነቱን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት።
6.10. ታካሚው ቢቀር ወይም የቀጠሮ ለውጥ ካደረገ ውል ተቀባይ በተለዋጭ ቀጠሮ ለ3 ወር ያልበለጠ በተለዋጭ ቀጠሮ የማስተናገድ ኃላፊነት አለበት፡፡
6.11. ውል ተቀባይ ለታካሚው አስፈላጊውን ደረሰኝ የመቁረጥና የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡
6.12. ሁሉም ክፍያ የሚከፈለው በኢትዮጵያ ብር ይሆናል፡፡
አንቀጽ ሰባት
ግብር
አንቀጽ ስምንት
የውል ስምምነት ማሻሻያ እና ማስተካከያ
8.1. ይህ ውል በሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች ስምምነት ሊሻሻል እና ሲስተካከል ይችላል፤
8.2. ምንም አይነት ማሻሻያ ወይም ማስተካከያ በሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች ካልተፈፀመ፤ በፅሁፍ ካልሆነ፤ቀን ካልተፃፈበት እና ዋናው ውል ካልተጠቀሰ በስተቀር እንደ ማሻሻያ ሊወሰድ አይችልም ::
አንቀጽ ዘጠኝ
ተግባራዊ የሚሆኑ ህጎች
አንቀጽ አስር
ቋንቋ
አንቀጽ አሥራ አንድ
የግጭት አፈታት
አንቀጽ አሥራ ሁለት
የውል ስምምነቱ የሚፈርስባቸው ምክንያቶች
12.1 በጤና ፈርስት ፕላስ በኩል ውል ሰጪው የ15 ቀን የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውሉን ሊያቋርጥ የሚችለው፡-
ሀ) ውል ተቀባይ ደንበኞችን በማጉላላት በተገቢው መንገድ ሳያስተናግድ ሲቀር፡፡
ለ) ውል ተቀባይ ለተቀበለው የላቦራቶሪ ትዕዛዝ አገልግሎቱን መስጠት ሳይችል ሲቀር፡፡
ሐ) ውል ተቀባይ በውሉ ውስጥ የተጠቀሱ ግዴታዎቹን ሳይወጣ ሲቀር።
መ) ውል ተቀባይ የሚጠበቅበትን አገልግሎት በተገቢው መንገድ ሳይሰጥ ሲቀር፡፡
ሸ) ውሉ እንዳይፈፀም የህግ ክልከላ ሲኖር
12.2 በውል ተቀባይ ሲቋረጥ፤- ውል ተቀባይ የ15 ቀን ቅድመ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የሚከተሉት ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት ሊያፈርስ ይችላል፡-
ሀ) ውል ሰጪ በውሉ ውስጥ የተመለከተውን ግዴታ በትክክል ሳይወጣ ሲቀር።
ለ) ጉድለቱን እንዲያስተካክል ውል ተቀባይ ገልጾለት ሳያስተካክል ሲቀር።
ሐ) ውል ተቀባይ የአገልግሎት ክፍያ የከፈሉበትን ተገቢ አገልግሎት ሳያገኙ ሲቀር።
መ) ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ውል ተቀባይ ግዴታውን መወጣት ሲያቅተው።
ሰ) የውል ሰጪ የቴክኒካል ድጋፍ አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ እገዛ ሳያደርግ ሲቀር፡፡
ረ) ውል ተቀባይ በራሱ ፈቃድ የ15 ቀን የፅሁፍ ማስንቀቂያ በመስጠት ሊያቋርጥ ይችላል፡፡
አንቀጽ አሥራ ሶስት
ውል ማሻሻያ
13.1. ውል ሰጪ ይህን ውል አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የማሻሻል ሙሉ መብት አለው፡፡
13.2. የተሻሻለውን ውል ለውል ተቀባይ በጤና ፈርስት ፕላስ ፕላትፎርም ዌብሳይት እና በውል ተቀባይ ባስመዘገበው ኢሜይል የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡
አንቀጽ አሥራ አራት
የውሉ ተፈፃሚነት
አንቀጽ አሥራ አምስት
ውሉ የሚፀናበት ጊዜ
አንቀጽ አሥራ ስድስት
የውሉ ህጋዊነት
16.1 ይህ ውል በውስጡ ላለው ቃል ለሚፈጠረው መብትና ግዴታ ግራ ቀኝ ተወያይተን በፍ/ብ/ህ/ቁ 1731 እና 2005 መሰረት ህግ አድርገን በመቀበል በፊርማችን እናረጋግጣለን፡፡
16.2. በዚህ ውል አገልግሎት ሰጪው አንቀፅ 2 ላይ የተዘረዘሩት የውል ሰነዶች እና የልውውጥ ኢሜይሎች የውሉ አካል ተደርገው በተጨማሪም አግባብነት ባላቸው የአገራችን ፍትሐብሔር ህጎች ይሸፈናሉ፡፡ ይህ ውል ከዛሬ ቀን May 27, 2026 ዓ.ም በሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች ምስክሮች ባሉበት ተፈርሟል፡፡
ውል ተቀባይ
ስም
ስልክ
ቀን May 27, 2026
Leave this empty:
Your legal name
Your email address
Signed by Abrham Assefa Signed On: August 13, 2024
Click on "Agree & Sign" to legally sign this document and agree to the WP E-Signature Terms of Use. If you have questions about the contents of this document, you can email the document owner.
Document Name: የጤና ፈርስት ፕላስ የውል ስምምነት ( Laboratory Vendor Agreement )
Click on "Agree & Sign" to legally sign this document and agree to the WP E-Signature Terms of Use.
Agree & Sign